Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ 11 ሰዎች መካከል ሁለቱ ጃፓናውያን ወደ ሃገራቸው ተሸኙ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ከተያዙ 11 ሰዎች መካከል ሁለቱ ጃፓናውያን ወደ ሃገራቸው መሸኘታቸውን አስታወቀ።

ሌሎች በቫይረሱ የተያዙ እና ከሰዎቹ ጋር ግንኙነት ነበራቸው የተባሉ ሰዎችም ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ነው የተባለው።

ከዚህ ቀደም በቫይረሱ ከተያዙት ሰዎች መካከል አራቱ የህመም ስሜት ማሳየት ማቆማቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ መግለጻቸው ይታወሳል።

የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከልም ከዛሬ ጀምሮ ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ ሰዎች በግዮን እና ስካይ ላይት ሆቴሎች ለ14 ቀናት ወደ ለይቶ ማቆያ ማስገባት ግዴታ ተጀምሯል።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.