Fana: At a Speed of Life!

የግሉ ዘርፍ የጤና ተቋማት የቤተሰብ ዕቅድ አሰጣጥን የሚመለከት ጥናት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 18 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የግሉ ዘርፍ የጤና ተቋማት የቤተሰብ ዕቅድ አሰጣጥን የሚመለከት ጥናት ይፋ ተደረገ።

ጥናቱ በሃንዝ አማካሪ የተሰራ ሲሆን፥ ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ደግሞ ጥናቱ እንዲደረግ ድጋፍ አድርጓል።

በጥናቱ መሰረት 12 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች በግሉ ዘርፍ የጤና ተቋማት የቤተሰብ ዕቅድ ክትትል እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

ጥናቱ ከትግራይ እና አፋር ክልሎች ውጪ በሁሉም ክልሎች የተደረገ ሲሆን ለጤና ሚኒስቴርና መሰል ተቋማት ትልቅ ግብአት ይሆናል ተብሏል።

በዘመን በየነ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.