Fana: At a Speed of Life!

በሦስት ክልሎች ሰላምና ልማት ጽ/ቤት አስተባባሪነት የተዘጋጀ የሰላም ጉባኤ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች ሰላምና ልማት ጽሕፈት ቤት አስተባባሪነት የተዘጋጀው የሰላም ጉባኤ በጋምቤላ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በሐይማኖት አባቶችና በሀገር ሽማግሌዎች ምርቃት የተጀመረው የሰላም ጉባኤ÷ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን ለማጠናከር ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡

የኦሮሚያ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች የጋራ የሰላምና የልማት ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ፍሮምሳ ሰለሞን ባቀረቡት ጽሑፍ÷ የሦስቱም ክልሎች ሕዝቦች የረጅም ጊዜ ቁርኝት አላቸው ብለዋል፡፡

ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቱ የሦስቱን ክልሎች ሕዝቦች በሰላምና በልማት ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሠራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የሕዝቦችን አብሮነትና ሰላም የሚያጠናክሩ እሴቶችን ለመጠበቅ በጋራ መሥራት ይገባል ማለታቸውንም የጋምቤላ ክልል ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.