የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና የህወሓት ታጣቂዎች አዛዦች ናይሮቢ ላይ ተገናኙ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና የህወሓት ታጣቂዎች አዛዦች ናይሮቢ ላይ ተገናኙ።
በሰላም ስምምነቱ ውስጥ በአምስት ቀን ውስጥ ወታደራዊ አመራሮች እንዲገናኙ በሚያዘው መሠረት የአዛዦቹ ውይይት ዛሬ በናይሮቢ ተጀምሯል ።
እስካሁን የስምምነቱ ሂደቱ በመልካም ሁኔታ እየሄደ ነው።