Fana: At a Speed of Life!

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለመካከለኛና ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ሥልጠና እየሰጠ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለመካከለኛና ከፍተኛ የሀገሪቱ ዲፕሎማቶች በውጭ ግንኙነትና በብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ ዙሪያ ስልጠና እየሰጠ ነው።

 

ስልጠናው በአፍሪካ አመራር ልህቀት ማዕከል ነው እየተሰጠ መሆኑን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።

 

በሥልጠናው የሀገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር፣ የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም የሚጋፋ የሌላውን የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ መመከት የሚያስችል ግንዛቤ እየተሰጠ ነው።

 

ሥልጠናውን እየሰጡ ያሉ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ፥ ኢትዮጵያውያን አንድትን ከፋፋይ አስተሳሰብ ራሳቸውን ማላቀቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

 

አያይዘውም ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ እንደ በለጸጉት ሀገራት ሃያል ባትሆንም በሃያላን ውሳኔ በሚመራ ዓለም ውስጥ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ሚናዋን በውል ማሳየት ያስፈልጋል ብለዋል።

 

 

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.