Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ 90 ሔክታር መሬት አጥረው የተቀመጡ ባለሀብቶች ውል ተቋረጠ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ 90 ሔክታር መሬት ያለምንም አገልግሎት አጥረው የተቀመጡ ባለሀብቶች ውል መቋረጡን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው ኃላፊ ቀነዓ ያደታ በሰጡት መግለጫ÷ በአዲስ አበባ መሬት አጥረው ለበርካታ ዓመታት ሳያለሙ በተቀመጡ ባለሃብቶች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷል ብለዋል፡፡

በከተማ አስተዳደሩ ከመሬት ልማት ጋር በተያያዘ በሚታዩ ችግሮች ላይ እየተወሰዱ ያሉ አስተዳደራዊ እርምጃዎችንም አብራርተዋል፡፡

ለአብነትም እስካሁን በአዲስ አበባ ከከተማ አስተዳደሩ 90 ሔክታር መሬት በሊዝ አዋጁ መሠረት ወስደው ሳያለሙ ለዓመታት አጥረው የተቀመጡ ባለሀብቶች ውል መቋረጡን ገልጸዋል፡፡

ውል የተቋረጠበት 90 ሔክተር መሬት በቅርቡ ለዓልሚዎች ግልጽ ጨረታ እንደሚወጣበትም ጠቁመዋል፡፡

በመሬት ልማትና አስተዳደር ላይ የሚታዩ ችግሮች መለየታቸውን ጠቁመው÷ ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታት የከተማ አስተዳደሩ አቅጣጫ ማስቀመጡንም ነው የተናገሩት፡፡

ግንባታ ጀምረው በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ያሉ ዓለሚዎችም እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም  ድረስ እንዲያጠናቅቁ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስታውቀዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.