Fana: At a Speed of Life!

በአለም ዋንጫ ሴኔጋል በኔዘርላንድስ ተሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሁለተኛው ቀን የኳታር የዓለም ዋንጫ ጨዋታ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል በኔዘርላንድስ 2 ለ 0 ተሸንፋለች፡፡

የኔዘርላንድስን የማሸነፊያ ጎሎች የፒኤስቪው አጥቂ ኮዲ ባክፖ እና የአያክሱ የመሀል ሜዳ ተጫዋች ዴቪ ኬላሰን አስቆጥረዋል፡፡

በጨዋታው የተሳኩ ሙከራዎችን ማድረግ የቻለችው ሴኔጋል ኔዘርላንድስን መፈተን ብትችልም በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች በተቆጠረባት ጎል ተሸንፋለች፡፡

የአጥቂያቸው ሳዲዮ ማኔ በጉዳት ምክንያት ከስብስቡ ውጭ መሆን ደግሞ ለሴኔጋል አጥቂ ክፍል መሳሳት ግልፅ ምክንያት ሆኖ ታይቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.