Fana: At a Speed of Life!

በሦስተኛው ቀን የዓለም ዋንጫ ውሎ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሦስተኛ ቀኑን በያዘው 22ኛው የዓለም ዋንጫ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይካሔዳሉ፡፡

በምድብ ሦስት የተደለደለችው አርጀንቲና ቀን 7 ሰአት ላይ ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር ትጫወታለች፡፡

ሊዮኔል ሜሲ የመጨረሻው በሆነው የዓለም ዋንጫ ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር በድል ለመመለስ ዛሬ አንድ ብሎ ይጀምራል።

በዚሁ ምድብ የደለደሉት ሜክሲኮ እና ፖላንድ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ፡፡

በምድብ አራት ደግሞ አፍሪካዊቷ ቱኒዚያ ከዴንማርክ ጋር ከቀትር በኋላ 10 ሰዓት ላይ ጨዋታዋን ታደርጋለች።

በዚሁ ምድብ ወሳኝ ተጫዋቾቿን በጉዳት ያጣችው ፈረንሳይ ከአውስትራሊያ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ትጫወታለች።

በኳታሩ የዓለም ዋንጫ እስካሁን አራት ጨዋታዎች ተደርገው በመሸናነፍ የተጠናቀቁ ሲሆን፥ 14 ጎሎች ደግሞ ከመረብ አርፈዋል።

ትናንት አመሻሽ እንግሊዝ ከኢራን ያደረጉትና በእንግሊዝ 6 ለ 2 አሸናፊነት የተጠናቀቀው ጨዋታ በውድድሩ በርካታ ጎሎች የተስተናገደበት ሆኗል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.