Fana: At a Speed of Life!

የሌ/ኮሎኔል አብዲሳ አጋ ሐውልት እና በስማቸው የተሰየመ ትምህርት ቤት ተመረቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሌተናል ኮሎኔል አብዲሳ አጋ ሐውልት እና በስማቸው የተሰየመ ትምህርት ቤት በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።

ሐውልቱን እና ትምህርት ቤቱን የመረቁት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፥ ሌተናል ኮሎኔል አብዲሳ አጋ የትውልዱ የሃገር ወዳድነት፣ የጀግንነትና የፅናት ተምሳሌት ነው ብለዋል።

የሌተናል ኮሎኔል አብዲሳ አጋ የጀግንነት ታሪክ የኢትዮጵያ ጀግንነት ታሪክ ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

አብዲሳ አጋ ዓለም ዓቀፍ ኢትዮጵያዊ ጀግና ሆኖ ሳለ በሚገባው ልክ ያልተዘመረለት ጀግና መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡

የሌተናል ኮሎኔል አብዲሳ አጋ ውርስ ስለሰንደቅ አላማ ክብር በፅናት መቆም፣ ኢትዮጵያን በየትኛውም ጥቅም አሳልፎ አለመስጠት፣ በየትኛውም ጫና ውስጥ ኢትዮጵያውያን የማንንበረከክ ህዝቦች መሆናችንን በተጨባጭ ማረጋገጥ፣ ነፃነትና አልበገር ባይነት የሉአላዊነታችንና የኢትዮጵያዊነታችን መለያ  መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.