Fana: At a Speed of Life!

አርጀንቲና ባልተጠበቀችው ሳዑዲ የዓለም ዋንጫውን በሽንፈት ጀምራዋለች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫው ሶስተኛ ቀን ውሎ ሳዑዲ ዓረቢያ ያልተጠበቀ ድል አስመዝግባለች።

ከደቡብ አሜሪካዋ አርጀንቲና ጋር የተጫወተችው ሳዑዲ ከመመራት ተነስታ 2 ለ 1 አሸንፋለች።

በጨዋታው ሊዮኔል መሲ በ10ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ባስቆጠረው ጎል አርጀንቲና 1 ለ 0 መምራት ብትችልም ሳዑዲዎች በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታውን ውጤት ቀይረውታል።

አል ሼሪ እና አል ዳውሳሪ በአሰልጣኝ ሄርቬ ሬናርድ ለምትመራው ሳዑዲ የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል።

አሰልጣኝ ሄርቬ ሬናርድ ከዚህ ቀደም ዛምቢያን እና አይቮሪኮስትን በመያዝ የአፍሪካ ዋንጫን ማሸነፍ ችለዋል።

በኳታሩ የዓለም ዋንጫ ሶስተኛ ቀን ውሎም ለዋንጫው ግምት ካገኙ ሀገራት መካከል አንደኛዋ የሆነችውን አርጀንቲናን በማሸነፍ ያልተጠበቀውን አሳክተዋል።

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.