Fana: At a Speed of Life!

ሚኒስቴሩ የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከሮችና ባለሙያዎችን ወደ ትግራይ መላኩን አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከሮችና የውሃ ባለሙያዎችን በጎንደር ሁመራ መስመር ወደ ትግራይ መላኩን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በተጨማሪም የውሃና ተያያዥ አገልግሎቶች ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች ከተለያዩ ቁሳቁስ ጋር መላካቸውን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የላከው መረጃ ያመላክታል፡፡

በሌላ በኩል ከዩኒሴፍ በድጋፍ የተገኙ በፀሃይ ሃይል የሚንቀሳቀሱ የውሃ መሳቢያ ፓምፖች በወልዲያ ቆቦ መስመር በኩል ወደ ትግራይ መላካቸው ተገልጿል፡፡

በትግራይ ክልል ሽረ ከሚገኙ የዩኒሴፍ ባለሙያዎች ጋር በመተባበር የውሃ መሳቢያ ፓምፖቹ አስቸኳይ የውሃ አቅርቦት ለሚያስፈልጋቸው የማከፋፈልና መሳሪያዎቹን የመግጠም ስራ እንደሚሰራ ተጠቁሟል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.