Fana: At a Speed of Life!

ፖላንድ ሳዑዲ ዓረቢያን 2 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ በምድብ ሶስት የሚገኙት ፖላንድ እና ሳዑዲ ዓረቢያ የሁለተኛ ዙር ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
በዚህም ፖላንድ ሳዑዲ ዓረቢያን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነጥቧን ወደ አራት ከፍ ማድረግ ችላለች፡፡
በተቃራኒው በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ጥሩ ተንቀሳቅሳ አርጀንቲናን ያሸነፈችው ሳዑዲ በነበረችበት ሶስት ነጥብ ላይ ተገትታለች፡፡
ሳዑዲ ዓረቢያ በመጀመሪያ አጋማሽ ያገኘችውን የፍጹም ቅጣት ምት ሳትጠቀምበት ቀርታለች፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.