Fana: At a Speed of Life!

ስፔንና ጀርመን አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) – የምድባቸውን ሁለተኛ ጨዋታ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ያደረጉት ስፔንና ጀርመን ሳይሸናነፉ ቀርተዋል።

ሁለቱ ቡድኖች 90 ደቂቃውን 1ለ1 በሆነ ውጤት አጠናቀዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ጀርመን በአንድ ነጠብ በምድቧ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ስፔን በአንፃሩ በ4 ነጥብ ምድቡን አየመራች ትገኛለች።

በዚህ ምድብ ሚገኙት ጃፓንና ኮስታሪካ እኩል ሶስት ነጥብ አላቸው።

ጀርመን የምድቧን የመጀመሪያ ጨዋት በሽንፈት የጀመረች ሲሆን ስፔን በአንፃሩ በሰፊ ጎል ልዩነት ማሸነፏ የሚታወስ ነው።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.