Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ ደረጃዎች ድርጅት ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሔደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 67ኛው የአፍሪካ ደረጃዎች ድርጅት ጉባዔ በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ እየተካሔደ ነው።

“የጥራት ሚና ለኢንዱስትሪ ዕድገት” በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሔደ በሚገኘው ጉባዔ ላይ ከ20 በላይ ከአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ባለድርሻ አካለት አየተሳተፉ ነው።

ጉባዔው በአራት ቀናት ቆይታው ምርቶችን ወደ ዓለም ገበያ ለማምጣት በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ እንደሚመክር ይጠበቃል፡፡

ጉባዔው በኢትዮጵያ መካሔዱ ለሀገሪቱ ገፅታ ግንባታ ከሚኖረው ሚና ባሻገር አህጉራዊ ግንኙትን እንደሚያጠናክር ተገልጿል፡፡

የአፍሪካ ደረጃዎች ድርጅት በፈረንጆቹ በ1977 ነው የተቋቋመው፡፡

በሳሙኤል ወርቃየሁ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.