Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለሌማት ትሩፋት አበርክቶ እያደረጉ ያሉ እናትን ሥራ ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሌማት ትሩፋት አበርክቶ እያደረጉ ያሉ እናትን ሥራ ጎብኝተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷በከተማችን ባላቸው ውስን ቦታ ላይ በጓሮ አትክልቶች፣ በዶሮ እና ከብት እርባታ፣ እንዲሁም በንብ ማነብና በሌሎችም የሌማት ትሩፋቶች የቤተሰባቸውን የምግብ አቅርቦት ከማረጋገጥ አልፎ ለአከባቢው ማኅበረሰብ ማቅረብ የቻሉ እማወራ ጎብኝተናል ብለዋል፡፡

በቤተሰብ ደረጃ በምግብ ራስን መቻል በሀገር ደረጃ በምግብ ራስን ለመቻል ለምናደርገው ጥረት መሠረት ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.