በዓለም ዋንጫ አፍሪካዊቷ ሴኔጋል እና ኔዘርላንድስ ጥሎ ማለፉን ተቀላቀሉ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኳታር ዓለም ዋንጫ ምሽት 12 ሰዓት ኔዘርላንድስ ከኳታር እንዲሁም ሴኔጋል ከኢኳዶር ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡
በጨዋታው አፍሪካዊቷ ሴኔጋል ኢኳዶርን 2 ለ 1 አሸንፋለች፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረገ ጨዋታ ደግሞ ኔዘርላንድስ ኳታርን 2 ለ 0 አሸንፋለች፡፡
በዚህም ሴኔጋል እና ኔዘርላንድስ ጥሎ ማለፉን መቀላቀላቸውን አረጋግጠዋል፡፡
በዓለም ዋንጫ ምሽት 4 ሰዓት የፖለቲካ ተቀናቃኞቹ ኢራን እና አሜሪካ ከ24 ዓመታት በኋላ የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡