Fana: At a Speed of Life!

ለአይደር ሪፈራል ሆስፒታል የተለያዩ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበበ፣ ሕዳር 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አቀፉ ህጻናት መርጃ ድርጅት (የኒሴፍ) መቀሌ ለሚገኘው አይደር ሪፈራል ሆስፒታል የተለያዩ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

የኒሴፍ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ እንደገለጸው÷በትግራይ ክልል የሕክምና መሳሪያዎችን በተለያዩ አካባቢዎች የማሰራጨቱ ሒደት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

በዚህ መሰረትም በትናንትናው ዕለት ለአይደር ሪፈራል ሆስፒታል ለድንገተኛ ህክምና የሚያገለግሉ የመመርመሪያ ኪቶች እና የተለያዩ መድሃኒቶች ድጋፍ ማድረጉን ጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም የማዋለጃ መሳሪያዎች፣ አስቸኳይ እርዳታ ለሚስፈልጋቸው ህጻናትና እናቶች የሚውል አልሚ ምግብ እና ወተት እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ ግብዓቶችን ማስረከቡን ድርጅቱ አስታውቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.