Fana: At a Speed of Life!

በአዲስ አበባ አርማ ወርሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማድረግ ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 20 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ የሚገኘው አርማ ወርሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በነገው ዕለት የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማድረግ ሊጀምር ነው፡፡

አሁን ላይ በሃገሪቱ በብቸኝነት ምርመራ ከሚያደርገው ከኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በተጨማሪ አርማ ወርሃንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማድረግ እንደሚጀምር የኢንስቲትዩ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ደጅይጥኑ ሙላው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

ለምርመራው የሚሆኑ የላብራቶሪ ቁሳቁሶች እና የሰው ሃይል መሟላታቸውንም ተናግረዋል፡፡

ምርመራውም እንደ ሃገር ያለውን የመመርመሪያ ቦታ ለማስፋት ያለመ እንደሆነ ደጅ ይጥኑ ሙላው ተናግረዋል፡፡

 

በፌቨን ቢሻው

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.