Fana: At a Speed of Life!

በጋምቤላ ክልል የሙስና ወንጀልን መከላከል የሚያስችል ኮሚቴ ተቋቋመ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ክልል የሙስና ወንጀልን ለመከላከል እና የወንጀሉን ተዋንያን ተጠያቂ ለማድረግ የሚያስችል ሰባት አባላት ያሉት ክልላዊ ኮሚቴ ተቋቁሟል።

ኮሚቴው በተለያዩ መዋቅሮች በተደራጀ መልኩ የሚፈፀም ሙስናን በመከላከል ወንጀለኞች ለሕግ ቀርበው ተጠያቂ እንዲሆኑ የሚያግዝ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

የፀረ ሙስና ክልላዊ ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት በብቃት እንዲወጣና ትርጉም ያለው ውጤት እንዲያመጣ ህብረተሰቡ ሙሉ ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል፡፡

ህብረተሰቡ የሙስና ተዋንያንን በተመለከተ ያለውን መረጃ በቀጣይ ቀናት ኮሚቴው ይፋ በሚያደርጋቸው አድራሻዎች በመላክ ሙስናን ለማጥፋት በሚደረገው ትግል ንቁ ተሳታፊ እንዲሆንም ተጠይቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.