Fana: At a Speed of Life!

ዲፕሎማቶች በአማራ ክልል የአምራች ኢንዱስትሪዎችን ጎበኙ

አዲስ አበበ፣ ሕዳር 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ሀገራት ኢትዮጵያን የሚወክሉ ዲፕሎማቶች በአማራ ክልል የአምራች ኢንደስትሪዎችን ጎበኙ።

ለቀናት የተለያዩ ስልጠናዎች የወሰዱት ዲፕሎማቶቹ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡልልታ በተገኙበት በደብረብረሃን ያሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን እና የተለያዩ ፋብሪካዎችን ጎብኝተዋል።

የጉብኝት መርሐ ግብሩ ዲፕሎማቶቹ ኢትዮጵያን በሚወክሉባቸው ሀገራት የውጭ ምንዛሬን እና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ምን መስራት እንዳለባቸው ግንዛቤ መፍጠርን ያለመ ነው ተብሏል።

ዲፕሎማቶች ሀገሪቷ ያላትን የመልማት አቅምና የአምራች ኢንዱስትሪው ያለበትን ደረጃ ማየት የሚያስችላቸውን ጉብኝት ትናንት በኦሮሚያ ክልል ጉብኝት ማካሄዳቸው ተመላክቷል፡፡

በሀብታሙ ተክለስላሴ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.