Fana: At a Speed of Life!

አርጀንቲና አውስትራሊያን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) -አርጀንቲና አውስትራሊያን በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቀለች።

ምሽት አራት ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ አርጀንቲና አውስትራሊያን 2ለ1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።

ለአርጀንቲና ጎሎቹን ሌዮኔል ሜሲ በ35ኛው እንዲሁም ጁሊያን አለቫሬዝ በ57ኛው ደቂቃዎች ላይ አስቆጥረዋል።

የአውስትራሊያን ብቸኛ ጎል በ77ኛው ደቂቃ ላይ የአርጀንቲናው ኤንዞ ፈርናንዴዝ በራሱ ጎል ላይ አስቆጥሯል።

ቀደም ብሎ 12 ሰዓት ላይ በተደረገ ጨዋታ ኔዘርላንድስ አሜሪካን 3ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀሏ ይታወሳል።

በቀጣይ አርጀንቲና ኔዘርላንድስን የምትገጥም ይሆናል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.