Fana: At a Speed of Life!

የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመራ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት በዛሬው ዕለት ኤርትራ አስመራ ገብተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ የኤርትራ አቻቸው ኢሳያስ አፈወርቂ  ባቀረቡላቸው ግብዣ መሰረት ነው ለስራ ጉብኝት ኤርትራ የገቡት፡፡

ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ እና ልዑካቸው አስመራ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ለሁለት ቀናት በአስመራ የስራ ጉብኝት የሚያደርጉ መሆኑንም የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል አስታውቀዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.