Fana: At a Speed of Life!

ዓለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲያሳድጉ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምስራቅ አፍሪካ የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ ዳንኤል እንድሪስ ዓለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ድጋፍ እንዲያሳድጉ ጥሪ አቀረቡ ፡፡
 
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከተመድ የምስራቅ አፍሪካ የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ ዳንኤል እንድሪስ ጋር ተወያይተዋል፡፡
 
በውይይታቸውም በኢትዮጵያ በተለያዩ ምክንያቶች ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች እየተደረጉ በሚገኙ የሰብዓዊ እርዳታዎች ዙሪያ መምከራቸውን አምባሳደሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡
 
በተመድ የምስራቅ አፍሪካ የሰብዓዊ እርዳታ አስተባባሪ ዳንኤል እንድሪስ÷የመንግስታቱ ድርጅት ኤጀንሲዎች እና ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን የሰብዓዊ ድጋፍ እንዲያሳድጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.