Fana: At a Speed of Life!

ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 150 የውሃ መሳቢያ ፓምፖች ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ሚኒስቴር ለበጋ መስኖ ልማት አገልግሎት የሚውሉ 150 የውሃ መሳቢያ ፓምፖችን ለደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ድጋፍ አድርጓል።

የውሃ መሳቢያ ፓምፖቹን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ወጌሾ በሚኒስቴሩ ዋና መሥሪያ ቤት ተገኝተው ከኢንጂነር አይሻ መሐመድ ተረክበዋል፡፡

ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደገለጹት÷ ሚኒስቴሩ በቀጣይ የክልሉን የልማት እንቅስቃሴ ይደግፋል፡፡

ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በበኩላቸው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያደረገው ድጋፍ በክልሉ እየተተገበረ ላለው የልማት ሥራ አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመራኦል ከድር

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.