Fana: At a Speed of Life!

በዓለም ዋንጫው ሞሮኮ እና ፈረንሳይ ዛሬ በግማሽ ፍጻሜው ይጫወታሉ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት አንድ ጨዋታ ይደረጋል።
 
አፍሪካዊቷ ሞሮኮ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከፈረንሳይ ጋር ለፍጻሜ ለመድረስ ትጫወታለች፡፡
 
ሁለቱ ቡድኖች በዓለም ዋንጫ በነጥብ ጨዋታ ሲገናኙ የምሽቱ የመጀመሪያቸው ይሆናል።
 
የጨዋታው አሸናፊ ከአርጀንቲና ጋር ለፍጻሜ የፊታችን እሑድ ይጫወታል።
 
ትናንት ምሽት በተደረገ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ አርጀንቲና ክሮሺያን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለፍጻሜ ማለፏ ይታወሳል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.