Fana: At a Speed of Life!

በኪንሻሳ ከባድ ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት ከ120 በላይ ሰዎች ለህልፈት ተዳረጉ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ዋና ከተማ ኪንሻሳ ከባድ ዝናብ ባስከተለው የጎርፍ እና የመሬት መንሸራተት ከ120 በላይ ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ በርካቶች መቁሰላቸው ተገልጿል።

በአደጋው በኪንሻሳ ብቻ 24 መንደሮች ተጎድተዋል።

በጎርፉ ሳቢያ ቤቶችን ጨምሮ በርካታ መንገዶች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፥ በደቡባዊ ሞንት ንጋፉላ ወረዳ በመሬት መንሸራተት ምክንያት ዋና ከተማዋን ከአትላንቲክ ውቅያኖስ የማታዲ ወደብ ጋር የሚያገናኘው ቁልፍ የአቅርቦት መስመር መቁረጡም ተነግሯል።

በዋሺንግተን በሚካሄደው የአፍሪካ – አሜሪካ ጉባኤ ላይ የተሳተፉት ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሼሲኪዲ ለሟች ቤተሰቦች የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.