ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ማሻሻያዎችን ስለመደገፍ ከዓለም ባንክ ቡድን ፕሬዚዳንት ዴቪድ ማልፓስ ጋር ጥሩ ውይይት አድርገናል ሲሉ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ የሠላም መስፈን ምርታማነትን እና የስራ ዕድል ፈጠራን የሚያጎለብት የኢኮኖሚ ሽግግር አጀንዳን ለማፋጠን እድል ይሰጣል ሲሉ ገልጸዋል፡፡