ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከአሜሪካ ንግድ ተወካይ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካ ንግድ ተወካይ አምባሳደር ካትሪን ታይን ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ከአሜሪካ- አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከአሜሪካ የንግድ ተወካይ አምባሳደር ካትሪን ታይን ጋር መምከራቸውን አንስተዋል፡፡
በውይይታቸውም የሁለቱን ሀገራት የንግድ ግንኙነት ማስፋፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ጥሩ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቁመዋል፡፡