Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ የአፍሪካ ሰብዓዊ ኤጀንሲን ለማቋቋም ስላለው ጥረት መከሩ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለ ወርቅ ዘውዴ የአፍሪካ ሰብዓዊ ኤጀንሲን ለማቋቋም ስላለው ጥረት ለአፍሪካ ኅብረት እና ለተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዳይሬክተር ጋር መክረዋል፡፡

ፕሬዚዳንቷ ÷ በአፍሪካ የሥነ-ሕዝብ ዕድገት ፣ እንዲሁም በትምህርትና በጤናው ዘርፍ አገልግሎት ተደራሽነት ላይ ከኮሚሽኑ ዳይሬክተር ማቤንጌ ንጎም ጋር መምከራቸውም ነው የተገለጸው፡፡

በውይይታቸው የትምህርትና የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን በተለይ ለልጆገረዶች ለማቅረብ በሚገጥሙ ተግዳሮቶች ላይም እንደመከሩ ከፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በተመሳሳይ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ በአሜሪካ የሚኘው ዳያስፖራው ማኅበረሰብ ያቋቋመው የ”ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ” መሥራቾች ከሆኑት አንዱንና የድርጅቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ፍሥሃ እሸቱ በጽኅፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ድርጅቱ በኢኮኖሚ ልኅቀት ለማምጣት፣ ረሃብን ለመዋጋት ብሎም የገበሬውን የአኗኗር ሥርዓት ለመለወጥ በግብርና፣ በኢ- ኮሜርስና በአግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ ተሰማርቶ እየሰራ ይገኛል፡፡

ድርጅቱ ‘ኑ አብረን እንሥራ’ የሚል አክሲዮን እንደሚያንቀሳቅስም በመረጃው ተመልክቷል፡፡

ፕሬዝደንት ሣኅለወርቅ ዘውዴም ድርጅቱ እየሠራ ስላለው ሥራ አመስግነው ጥረታቸውን እንደሚደግፉ በመግለጽ አበረታተዋቸዋል።

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.