የአረንጓዴ አሻራ እንክብካቤ ዘመቻ በኦሮሚያ ክልል ተጀመረ
አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 11 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአረንጓዴ አሻራ እንክብካቤ ዘመቻ በኦሮሚያ ክልል ተጀምሯል፡፡
በሀገሪቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር እንደ ሀገር ከተተከሉት 25 ቢሊዮን ችግኞች 13 ነጥብ 6 ቢሊየን ችግኞች በኦሮሚያ እንደተተከሉ ተገልጿል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ እንክብካቤ ዘመቻው በምስራቅ ባሌ ዞን ግንዲር ከተማ እና በጅማ ዞን ሰቃ ጮቆርሳ ወረዳ መጀመሩን የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡