Fana: At a Speed of Life!

እስካሁን ከ31 በላይ በሆኑ ከተሞች የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም ጀምሯል

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቴሌኮም አገልግሎት ተቋርጦባቸው ከነበሩ አካባቢዎች መካከል እስካሁን ከ31 በላይ በሚሆኑ ከተሞች አገልግሎቱ ዳግም መጀመሩን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ፡፡

በዚሁ መሰረት፡-

👉 በዛሬው ዕለት መቀሌ፣ ውቅሮ፣ ኪሓ እና አባላ የቴሌኮም አገልግሎት አግኝተዋል፡፡

👉 ከዚህ ቀደም 27 ከተሞች አገልግሎቱን ማግኘታቸው ይታወሳል፡፡

👉 በግጭቱ ምክንያት የቴሌኮም አገልግሎት ከተቋረጠባቸው አካባቢዎች መካከል እስካሁን ከ31 በላይ ከተሞች ዳግም አገልግሎት አግኝተዋል፡፡

👉 አገልግሎቱን መልሶ ለማስጀመር ዘጠኝ የቴክኒካል ቡድኖች በአራት አቅጣጫዎች ተሰማርተዋል፡፡

👉 በዚህም ከ981 ኪሎ ሜትር በላይ የፋይበር መገናኛ መስመር ጥገና ማከናወን ተችሏል፡፡

👉 90 የሞባይል ሳይቶችን ዳግም በማገናኘት የስልክ ጥሪ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል፡፡

👉 61 የባንክ ቅርንጫፎች ዳግም ወደ አገልግሎት የሚመለሱበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡

👉 የቴሌኮም አገልግሎቱን በሙሉ አቅም ለማስቀጠል የጥገና ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡

👉 አገልግሎቱ ከረጅም ጊዜ በኋላ እንደመጀሩ የኔትወርክ መጨናነቅ ሊኖር ስለሚችል ደንበኞች ሁኔታውን እንዲገነዘቡ የኩባንያው ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ጠይቀዋል፡፡

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.