Fana: At a Speed of Life!

ጸደይ ባንክ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡ 24 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መድረሱን ገለጸ

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጸደይ ባንክ በ2014 ዓ.ም ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡ 24 ነጥብ 5 ቢሊየን መድረሱን የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ገልጸዋል፡፡

ፀደይ ባንክ የባለ አክሲዮኖች 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በባህር ዳር ከተማ እያካሄደ ነው።

በ2014 ዓ.ም ባንኩ ከተለያዩ መለኪያዎች አንፃር አበረታች ውጤት እንዳስመዘገበም አቶ ገዱ የተናገሩት።

አያይዘውም የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ በ12 በመቶ አድጎ 24 ነጥብ 5 ቢሊየን ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ መድረሱንም ገልጸዋል።

ሰኔ 2020/21 በተደረገ ሪፖርት ባንኩ 38 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ካፒታል እንዳስመዘገበና 9 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ጠቅላላ የተጣራ ካፒታል ማካበቱንም አንስተዋል፡፡

ባንኩ የቁጠባ መጠኑን 28 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ያደረሰ ሲሆን 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ጠቅላላ ትርፍም አግኝቷል ብለዋል።

ካለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር በ29 በመቶ እድገት አሳይቷል የተባለ ሲሆን ለበርካታ ዜጎችም የብድር አገልግሎት መስጠት መቻሉም ተነስቷል፡፡

በሙሉጌታ ደሴ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.