የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ምስረታ ጉባኤውን እያካሄደ ነው
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብሔረሰቦች ምክር ቤት ምስረታ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡
በጉባኤው የመስራች ጉባኤ አባላት፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
በዛሬው የክልሉ ብሔረሰቦች ምክርቤት ምስረታ ዋና አፈ ጉባኤና ምክትል አፈ ጉባኤዎች የሚመረጡ መሆኑን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡