Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ ለበዓሉ የመብራት መቆራረጥና የውሃ ችግር እንዳያጋጥም የተቀናጀ ግብረ ኃይል ተቋቁሟል

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 26 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በበዓል የመብራት መቆራረጥና የውሃ ችግር እንዳያጋጥም የተቀናጀ ግብረ- ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱን የከተማ አስተዳደሩ ሥራ አስኪያጅ ጽኅፈት ቤት ገለጸ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ ጽኅፈት ቤት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ በሰጡት መግለጫ ÷ የፊታችን ቅዳሜ ለሚከበረው የገና በዓል የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት የተሳለጠ አገልግሎት ለነዋሪው ለማቅረብ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡

በተለይም የመብራት መቆራረጥና የውሃ ችግር እንዳያጋጥም ከወዲሁ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው ÷ የተቀናጀ ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱን አመክተዋል፡፡

የእነዚህ አገልግሎቶች ችግር ቢያጋጥምም ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል ነው ያሉት።

ሕብረተሰቡ የእሳት አደጋ እንዳይከሰት ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት አሳስበው ÷ አደጋ ቢያጋጥም እንኳን የእሳትና ድንገተኛ አደጋ በዋናው መሥሪያ ቤቱና በዘጠኙም ቅርንጫፎቹ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅትም ለበዓሉ ጤናማ የሆነ ሥጋ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ነው የገለጹት፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.