Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች የገና በዓልን በምገባ ማዕከል ከሚገኙ ወገኖችጋር አሳለፉ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የገና በዓልን በምገባ ማዕከል ከሚገኙ ወገኖች ጋር አሳልፈዋል፡፡

ከንቲባዋ በመዲናዋ ከሚገኙ ምገባ ማዕከሎች አንዱ በሆነው አሙዲ የምገባ ማዕከል ነው ከከረዮ- ጌጃ ሰፈር ወገኖች ጋር በዓሉን ያሳለፉት ፡፡

ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው “ወገኖቻችንን በመመገብ እየተጋችሁ ያላችሁ በጎ አድራጊዎች ፣ አመራሮችና እናቶች ከልባችን እናመሰግናለን “ብለዋል፡፡

በዓሉ የይቅርታ ፣ የአብሮነት፣ የደስታ ፣ያማረና የሰላም እንዲሆንም ተመኝተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.