ከንቲባ አዳነች የገና በዓልን በምገባ ማዕከል ከሚገኙ ወገኖችጋር አሳለፉ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የገና በዓልን በምገባ ማዕከል ከሚገኙ ወገኖች ጋር አሳልፈዋል፡፡
ከንቲባዋ በመዲናዋ ከሚገኙ ምገባ ማዕከሎች አንዱ በሆነው አሙዲ የምገባ ማዕከል ነው ከከረዮ- ጌጃ ሰፈር ወገኖች ጋር በዓሉን ያሳለፉት ፡፡
ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው “ወገኖቻችንን በመመገብ እየተጋችሁ ያላችሁ በጎ አድራጊዎች ፣ አመራሮችና እናቶች ከልባችን እናመሰግናለን “ብለዋል፡፡
በዓሉ የይቅርታ ፣ የአብሮነት፣ የደስታ ፣ያማረና የሰላም እንዲሆንም ተመኝተዋል፡፡