Fana: At a Speed of Life!

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአፍሪካ ጉብኝታቸውን በኢትዮጵያ ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቅርቡ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ቺን ጋንግ በስልጣን ዘመናቸው የመጀመሪያ የሆነውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ኢትዮጵያ ገብተዋል።

ቺን ጋንግ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ÷ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን እና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በአምስት የአፍሪካ ሀገራት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሚያደርጉት የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር÷ ኢትዮጵያን የጉብኝታቸው መጀመሪያ አድርገዋል።

በኢትዮጵያ ቆይታቸውም የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ ግንኙነት ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሳደግ የሚረዱ ውይይቶች ያደርጋሉ ተብሏል።

ቺን ጋንግ÷ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ ከአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማኸመት እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ጋር እንደሚመክሩ ይጠበቃል።

በትዕግሥት አስማማው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.