Fana: At a Speed of Life!

በዓመት 1 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚገጣጠሙበት ፋብሪካ ከ3 ወራት በኋላ ሥራ ይጀምራል

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደብረ ብርሃን ከተማ በዓመት 1 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መገጣጠም የሚያስችል የተሽከርካሪ መገጣጠሚያ ፋብሪካ ከሦስት ወራት በኋላ ሥራ ይጀምራል፡፡

በደብረ ብርሃን ከተማ ለተገነባው የኤሌክትሪክ መገጣጠሚያ ፋብሪካ 2 ቢሊየን ብር ወጪ ተደርጓል፡፡

የፋሪካው ባለቤት አቶ በላይነህ ክንዴ ለፋናብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ፋብሪካው ከሦስት ወር በኋላ ወደማምረት ሥራ ይገባል፡፡

ፋብሪካው በዓመት 1ሺህ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን የመገጣጠም አቅም እንዳለው ገልጸው÷ ከሦስት ወራት በኋላ ወደ ሥራ ሲገባ በዚህ ዓመት ከ250 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እንደሚገጣጠሙ ተናግረዋል፡፡

ፋብሪካው ለ500 ሰዎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርም ተመላክቷል፡፡

በዘላለም ገበየሁ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.