Fana: At a Speed of Life!

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከ3 ሺህ በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጅማ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 206 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ዕለት ያስመረቃቸው÷ በሕክምና፣ በተፈጥሮ ሣይንስ፣ በማኅበራዊ ሣይንስ እና በሌሎች የትምህርት ዘርፎች በተለያየ መርሐ ግብር ትምርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ናቸው፡፡

ከተመራቂዎቹ መካከል 296 ያህሉ በሕክምና ሲሆን÷ ይህም ዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሐኪሞች ሲያስመርቅ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል ከዛሬ ተመራቂዎቹ መካከል 24 ያህሉ በሦስተኛ ዲግሪ ትምህርትታቸውን የተከታተሉ ናቸው፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ እንደገለጹት÷ የሕክምና ተመራቂዎች ከራስ በፊት ሕዝባቸውንና ሀገራቸውን በማስቀደም የገቡትን ቃል ኪዳን በትጋት እንዲወጡ ጠይቀዋል።

በሙክታር ጠሃ እና አብዱራህማን መሃመድ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.