Fana: At a Speed of Life!

በሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ማለዳ በሕንድ በተካሄደው የሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ።

በሴቶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 8ኛ ተከታትለው በመግባት በበላይት አጠናቀዋል፡፡

በውድድሩ አትሌት አንቺዓለም ሃይማኖት 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፋለች፡፡

አትሌት ረሂማ ቱሳ እና አትሌት ለተብርሃን ኃይላይ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡

በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2 ሰዓት ከ7 ደቂቃ ከ32 ሰከንድ በመግባት የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል አሸንፏል፡፡

ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ሮኖ 2ኛ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ኃይሉ ዘውዱ 3ኛ ደረጃን ይዘው ውድድሩን ጨርሰዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.