Fana: At a Speed of Life!

መስዋዕትነት ለከፈሉ ዓርበኞች ልጆች የሕፃናት መርጃ ማዕከል የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኅልውና ዘመቻው ለሀገር መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግኖች ዓርበኞች ልጆች ማሳደጊያ የሚውል የሕፃናት መርጃ ማዕከል በጎንደር ከተማ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ፡፡

የመርጃ ማዕከሉ የመሰረት ድጋይ በጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዘውዱ ማለደ የተቀመጠ ሲሆን ÷ “ባንቺ የሕፃናት መርጃ ማዕከል” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

የግንባታው ወጪ የሚሸፈነው ባንችአምላክ ይልማ በተባሉ ግለሰብ ሲሆን÷ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ደግሞ ለማዕከሉ ግንባታ የሚውል 1 ሺህ 500 ካሬ ሜትር መሬት ማስረከቡን የከተማው ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.