Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተቋርጦ የነበረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጥር 20 ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለቻን ላለበት ውድድር ተቋርጦ የነበረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 ውድድር ከፊታችን ጥር 20 ቀን ጀምሮ በአዳማ ከተማ መካሄዱ እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡

በዚህ መሰረትም ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች የ12ኛ ሳምንቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና ቅዳሜ ጥር 20 ቀን 2015 ዓ.ም እንዲሁም የ11ኛ ሳምንቱ ወላይታ ድቻ ከሲዳማ ቡና እሁድ ጥር 21 ቀን 2015 ዓ.ም 9፡00 ሰዓት ይካሄዳሉ፡፡

በተጨማሪም ከ14ኛ እስከ 19ኛ ሳምንት ያሉ ጨዋታዎች ከጥር 23 እስከ መጋቢት 03 ቀን 2015 ዓ.ም ከሐሙስ እስከ እሁድ ባሉ ቀናት በ9 እና 12 ሰዓት እንደሚካሄዱ የኢትዮጵያፕሪሚየር ሊግ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.