Fana: At a Speed of Life!

ባሕር ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ድርጅት በ6 ወራት 19 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በሥድስት ወራት 19 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።

ድርጅቱ የበጀት ዓመቱን የሥድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሮባ መገርሳ ÷ ባለፉት ሥድስት ወራት ድርጅቱ የ2 ነጥብ 4 ሚሊየን ቶን የኦፕሬሽን አገልግሎት መስጠቱን ገልጸዋል።

አቶ ሮባ ፥ ድርጅቱ 312 ሺህ ቶን ብትን እንዲሁም 4 ሺ 500 በኮንቴይነር የታሸገ ጭነት ማጓጓዙንም ነው የተናገሩ።

በኮንቴይነር ከተጓጓዙት ጭነቶች መካከል 3 ሺህ 79 ያህሉ በሀገር ውስጥ መታሸጋቸውን እንደጠቆሙም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

በአጠቃላይ ኢ.ባ.ት.ሎ.ድ ከላይ የተጠቀሱትን አገልግሎቶች ባለፉት ሥድስት ወራት አቅርቦ 19 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱም ነው የተመለከተው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.