Fana: At a Speed of Life!

አይ ሲ ቲ ፓርክን በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ለማስገባት ያለመ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አይ ሲ ቲ ፓርክን በሙሉ አቅሙና በአዲስ መልክ በተሰጠው ተልዕኮ መሠረት ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችል ውይይት ተካሄደ፡፡

ውይይቱን ያዘጋጀው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ነው፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልገሎትና ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባደረጉት ውይይት÷ የአይ ሲ ቲ ፓርኩን ወደ ሥራ ለማስገባት ቁልፍ መሠረተ ልማቶችን በቅንጅት ለማሟላት መክረዋል፡፡

በዚህም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትና የተቋም ደኅንነት ጥበቃ ለማስጀመር ከሁለቱ ተቋማት ጋር ከስምምነት ላይ መደረሱን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

አገልግሎቱን ለማሳለጥ ከሚመለከታቸው ሌሎች ተቋማት ጋር ተከታታይ ውይይት እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.