Fana: At a Speed of Life!

ቻይና የሠራችው “ሲ 919” አውሮፕላን የመጀመሪያ መደበኛ በረራውን በስኬት አከናወነ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በራስ አቅም የሠራችው “ሲ 919” የመንገደኞች አውሮፕላን ከሙከራ በኋላ ትናንት የመጀመሪያ መደበኛው በረራውን በስኬት አከናውኗል፡፡

አውሮፕላኑ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ 26 ቀን 2022 የ100 ሰዓታት የሙከራ በረራ ማካሄዱን አስታውሶ ሲጂቲ ኤን ዘግቧል፡፡

ንብረትነቱ የቻይና ምሥራቃዊ ዓየር መንገድ የሆነው አውሮፕላኑ÷ ከሻንጋይ ሆንግኪያኦ አውሮፕላን ማረፊያ ተነሰቶ ናንቻንግ ቻንቤይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ያደረገው በረራ በስኬት መጠናቀቁ ተነግሯል።

አውሮፕላኑ በቻይና የንግድ አውሮፕላኖች ማምረቻ ኮርፖሬሽን መሠራቱ ተመልክቷል፡፡

የቻይናው ሲቪል አቪዬሽን አስተዳደር የቻይና ምሥራቃዊ ዓየር መንገድ ግዙፉን አውሮፕላን በስኬት ማብረር ስለመቻሉ ምርመራ ካካሄደ በኋላ÷ የሥራ ፈቃድ እንደሚሠጠው የዓየር መንገዱ የጂያንግዚ ምርት ማዘዣ ማዕከል ዳይሬክተር ው ጂንጁን ተናግረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.