Fana: At a Speed of Life!

“ከብዙ ፈተናዎች ጋር እየተጋፈጥን ሳለ፣ኢኮኖሚያችን ጽኑ በሆነ መልኩ እየተጠናከረ ነው” – ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ ፣ ጥር 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከብዙ ፈተናዎች ጋር እየተጋፈጥን ሳለ፣ ኢኮኖሚያችን ጽኑ በሆነ መልኩ እየተጠናከረ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷ ይህን ይበልጥ አጠናክረን ለመቀጠል ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በትብብር ምርታማነት ላይ መሥራት አስፈላጊ ነው ብለዋል።

የቱሪዝም ዘርፉን ለማጎልበት የገበታ ለሀገር አካል በሆነው ሐላላ ኬላ ውብ ቦታ ላይ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያለፉትን ሥድስት ወራት አፈጻጸም በመገምገም ላይ መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.