Fana: At a Speed of Life!

ኮሚሽኑ ከተመድ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በአጋርነትና ትብብር ጉዳዮች ላይ ተወያየ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔራዊ የተሐድሶ ኮሚሽን ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር በአጋርነትና ትብብር ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የመጀመሪያ ዙር ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ ኮሚሽኑ ከተቋቋመ ጀምሮ በአደራጅ ኮሚቴው የተከናወኑ ተቋማዊ አደረጃጀቶች፣ የቀድሞ ተዋጊዎች መረጃ ማሰባሰቢያ ፎርማቶች እና የፕሮጀክት ዝግጅት ጉዳዮች ላይ ምክክር ተደርጓል፡፡

በቀጣይ በአጋርነት ሊሰሩ የሚገባቸው ጉዳዮች ተለይተው የጋራ መግባባት ላይ መደረሱንም ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢፌዴሪ የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ተጠሪነቱ ለሰላም ሚኒስቴር ሆኖ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 565 /2015 የተቋቋመ ነው።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.