Fana: At a Speed of Life!

ዓለም አቀፉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተግባር ቡድን 442 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተግባር ቡድን 442 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የህክምና ቁሳቁስ ለጤና ሚኒስቴር ድጋፍ አደረገ።

የዓለም አቀፉ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተግባር ቡድን ሊቀመንበር እንዳልካቸው ዘውዴ ÷ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፉን ለጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ማስረከባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ዶክተር ሊያ በበኩላቸው ÷ ቡድኑ ላደረገው ድጋፍ ያመሠገኑ ሲሆን ፣ በሀገሪቱ ተከስቶ በነበረው ጦርነት ሳቢያ የወደሙ የጤና መሰረተ ልማቶችን ወደ ስራ ለማስገባት ለሚደረገውን ጥረት ዳያስፖራዎች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ዓለም አቀፉ የዳያስፖራ የተግባር ቡድን በፈረንጆቹ መጋቢት 2022 እንደተቋቋመ መረጃዎች ያሳያሉ።

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.