Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮ ቴሌኮምን በከፊል ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዛወር ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጣ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 3 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት ኢትዮ ቴሌኮምን በከፊል ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዛወር በድጋሚ ዓለም አቀፍ ጨረታ አወጣ።

አሁን የወጣው ጨረታ የኢትዮ ቴሌኮምን 45 በመቶ ድርሻ ለዓለም አቀፍ ባለሃብቶች ለማቅረብ ያለመ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ኩባንያዎችም የማይመለስ 20 ሺህ ዶላር እና መተማመኛ በ13 ቀናት ውስጥ ማቅረብ እንደሚችሉም ነው የገለጸው።

የጨረታ ሰነዳቸውን telecombid@mofed.gov.et በመግባት ማቅረብ እንደሚችሉ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.