Fana: At a Speed of Life!

በቀይ ባህር ሲጓዙ የነበሩ 383 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን ከሞት መታደግ ተቻለ

 

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀይ ባህር ወደ የመን ሲጓዙ የነበሩ 383 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን ከሞት መታደግ መቻሉን በጅቡቱ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡

በጅቡቲ 383 ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን ጭኖ ወደ የመን በመጓዝ ላይ የነበሩ ህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ ጀልባዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ተገልጿል፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪነት የተጠረጠሩ ግለሰቦችለፍርድ መቅረባቸውንም በጅቡቱ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኤምባሲው የጅቡቲ የባህር ዳርቻ ጥበቃ ሃይል ፍልሰተኛ ኢትዮጵያውያንን ለመታደግ ለሚያደርጓቸው ዘመቻዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.