Fana: At a Speed of Life!

የፓኪስታን ባለሐብቶች በኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ እንዲሰማሩ የኢንቨስትመንት አማራጭ ቀረበላቸው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፓኪስታን ባለሐብቶች በጤናው ዘርፍ መዋዕለ-ንዋያቸውን በኢትዮጵያ እንዲያፈሱ የኢንቨስትመንት አማራጭ ቀረበላቸው፡፡

ኢትዮጵያ አማራጮቹን ይፋ ያደረገችው በፓኪስታን በተካሄደው የፋርማሲ ቁሶች እና የጤና መጠበቂያ ምርቶች ኤክስፖ ላይ ነው፡፡

በኤክስፖው በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ዳንዔል ተሬሳ በፓኪስታን ላሆር ከተማ በተካሄደው “የፋርማ ኤክስፖ” የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝዋል፡፡

ልዑካን ቡድኑ በፋርማሲው ዘርፍ እና በጤና መጠበቂያ ምርቶች ላይ ከተሠማሩ ባለሐብቶች ጋርም ተወያይተዋል፡፡

በተጨማሪም ልዑካኑ ከሀገሪቷ ፌዴራላዊ እና ክልላዊ ንግድ ምክር ቤቶች ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሮች እንዲሁም ከሀገሪቷ የኢንቨስትመንት ማስታወቂያ ኤጀንሲ ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት ጋር መምከራቸውን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.